2008 ዓም10+last.pdf · 2008 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞ ግንባር...

24
የኢትዮዽያ ሕዝብ በኑሮ ውድነት እና በፍትህ እጦት ምክንያት በእርሀብ፣ በእስራት እና በስደት ላይ ይገኛል የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ምክር ቤት በጀርመን ተመሰርተ አዲሱ አመት 2008 .. ለኢትዮዽያውያን የነጻነት እና የሰላም ጊዜ እንዲሆን እንመኛለን 2008ዓ.ም.

Upload: dangngoc

Post on 07-Sep-2018

241 views

Category:

Documents


3 download

TRANSCRIPT

የኢትዮዽያ ሕዝብ በኑሮ ውድነት እና በፍትህ እጦት ምክንያት በእርሀብ፣ በእስራት እና በስደት ላይ ይገኛል

የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ምክር ቤት በጀርመን ተመሰርተ

አዲሱ አመት 2008 ዓ.ም. ለኢትዮዽያውያን የነጻነት እና የሰላም ጊዜ እንዲሆን እንመኛለን

2008 ዓ .ም.

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞ ግንባር ዘብ መደበኛ ስብሰባውን በፍራንክፈርት ከተማ

በ11/07/2015 በተሳካ ሁኔታ አካሄደ

(The regular meeting of EPPFG held successfully on 11/07/2015 in

Frankfurt)

ጎሕ መጽሔት

1 Goh magazine, July 2015, 2

ዋና ስራ አስኪያጅ ልዑል ቀስቅስ

ዋና አዘጋጆች ደሳለኝ አበባው አለሜ ቡቃያ

ም/አዘጋጅ ጌታቸው ሐይለማርያም አያኖ

ኤዲተር አለማየሁ ጥበቡ

ኮምፒውተር ፁሁፍ ፎዚያ ጫጮ

ግራፊክስ ሙሴ ቢሆነኝ በትረ

ካርቶኒስት & መፅሐት ስርጭት ሞሐመድ ባልቻ አብዱልሀኪም

ፎቶግራፍ ይህደጎ ሚካኤል ምኮንን

ፅሁፍ አስተባባሪ ምነወር አብድልዋሂድ ክማል

መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

General Manager Leul Keskis

Editors in Chief Desalegne Abebew

Alemie Bukaya

Assistant Editor in chief Getachew Hailemariam Ayano

Editor Alemayhu Tibebu

Computer Writing Foziya Chacho

Graphics Musie Bihonegn Betre

Cartoonist & Distributer Mohammed Balcha, Abdulhakim

Photographer Yihedego Michael Mekonnen

Organizer Minewer Abdulwahid Kemal

Getachew Hailemariam Ayano

Cartoonist & Distributer Mohammed Balcha, Abdulhakim

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

2 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

ማውጫ

የመጣጥፎች ይዘት ገጽ ነጻነታችን በእጃችን ነው፣ ህወሃት ካልተገረሰሰ እርሐቡም፣ እስሩም ይቀጥላል! ......................................................................... 3

ተነስ ወገኔ .................................................................................................................................................... 4

አንድ መሪ ኣላት ተብሎ የምትከበር አገር ............................................................................................................... 4

በተጭበረበረ የፖለቲካ ሽፋን የህግ የበላይነት ተቀብሯል ............................................................................................ 4

የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር እጦት መልስ የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው .................................................................... 5

ሃገራችንን ሃገር እናድርግ .................................................................................................................................. 5

የ 2007 ምርጫ ቢቀርስ................................................................................................................................... 6

የአማራን ዘር የማጥፋት ዘመቻ ........................................................................................................................... 6

ማስመሰል ይብቃን ......................................................................................................................................... 7

በወያኔ ድንክየ የፖለቲካ አስተሳሰብ ዕስከመቸ? ....................................................................................................... 7

የወያኔ ጥላቻ ፍሬ ........................................................................................................................................... 8

ያለፈውን ስርዓት መናፈቅ ................................................................................................................................. 8

የሕወሓት ማፊያ ቡድን ከምድረገጽ መጥፋት አለበት ................................................................................................ 9

መሪ አልባ አገር .............................................................................................................................................. 9

ኑሮ ተወደደ ................................................................................................................................................ 10

መሪ የሌለው ህዝብ ....................................................................................................................................... 11

የነጻነት ተስፋ .............................................................................................................................................. 11

Ethiopia is Stuck .................................................................................................................................... 12

The youth of Ethiopia ............................................................................................................................ 13

Ethnic politics is an existential threat to all Ethiopians ......................................................................... 14

What shall we do? ................................................................................................................................. 15

Weyane (TPLF) und die Verfassung ..................................................................................................... 16

አርበኛ የሚያሰኝህ ........................................................................................................................................ 19

ድምጽ የሌለው ጥይት.................................................................................................................................... 19

ዱላ ቅብብል (ለአሁኑ ገዢዎቻችን) ................................................................................................................... 19

ፍትህን ፍለጋ .............................................................................................................................................. 19

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

3 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

ርዕሰ አንቀፅ ኢትዮዽያ በዲሞክራሲ እና በምግብ እጥረት በአንደኝነት ላይ ትገኛለች

ሕወሃት ሁለት መገለጫዎች አሉት። የመጀመሪያው የጦር ሃይሉን በመተማመን፣ በጉልበት ስልጣን ላይ እንደተቆናጠጠ

ዘላለም እገዛለሁ ብሎ ማሰቡ ነው። የመሳሪያ ባለቤት በመሆኑ፣ የተቃወመኝን እያሰርኩ፣ ጠላቴን እየገደልኩ፣ እንዲሁም

ከተቃውሞ የማይታቀበውን እያስፈራራሁ ለረጅም ጊዜ እኖራለሁ ብሎ ያምናል። እዉነትም ህወሃት በከፊል ትክክል

ነበር፣ በጉልበት እያስፈራራ፣ እያሰረ፣ እየገደለ ለ25 አመታት ያለምንም ችግር ዘልቋል። ከራሱ ከህወሃት የተፈጠሩ የጦር

መኮንኖችን ብቻ ስልጣን ላይ አስቀምጦ፣ በሙስና እንዲዘፈቁ በማበረታታትና፣ የሚያማልል ስጦታ በመስጠት፣

እንዲሁም እነዚሁን የጦር መኮንኖች የወንጀል ተባባሪና መሪ በማድረግ የ”አብረን እንዝለቅ” ጨዋታ ተክኖበታል።

ሁለተኛው የህወሃት መገለጫ ደግሞ ከመንግስት ባለስልጣናት ያውም ከሚኒስትሮች የማይጠበቁ ዘረኝነት፣

ስግብግብነት፣ ውሸትና፣ የሞራል ዝቅጠት ነው። አብዛኞቹ ባለስልጣናት በዘረኝነት ዛር የሰከሩ ወፈፌዎች ናቸው።

የራሳቸውን ብሄር “ወርቅ” በማለት የሚያሞካሹ፣ ሌላውን ብሄረሰብ ግን “ትምክህተኛ፣ አክራሪ፣ ብሄርተኛ” የሚል

ታፔላ በመለጠፍ በጅምላ የሚሳደቡ ናቸው። እነሱ እንደሚሉት ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ከ22 አመታት በኋላም

ቢሆን ከችግር፣ ረሃብና፣ እርዛት ኣልተላቀቀም። የህወሃት ባለስልጣናት ግን ገንዘብ ተርፏቸው በሚሊዮን የሚቆጠር

ዶላር ወደ ውጭ አገር እያሸሹ እንደሆነ አለም የሚያውቀው ሃቅ ነው። በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ይኸው ከ 24 አመት

የስልጣን ጊዜ በኋላም ከ24 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን እርዳታ ይፈልጋሉ። የህወሃት አሽከሮችና ጭፍሮቻቸው

በምግብ ራሳችንን ችለናል የሚል ልፈፋ ሲያሰሙ ከርመው ነበር። የታል ታዲያ? እርግጥ ነው የህወሃት ባለስልጣናት

ኪስ በ11 ሚሊዮን % አድጓል። የህዝቡ ኑሮ ግን 1% እንኳን ከፍ አላላም። እርግጥ ነው በህወሃት መንደር እና

ሎሌዎቻቸው ቤት ምግብ ተትረፍርፏል፣ በሱማሌ፣ በአፋርና፣ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች፣ የገበሬዎች የቤት እንስሳትና

የቀንድ ከብቶች ተረፍርፈዋል።

እንግዲህ ህወሃቶች ለስልጣናቸው ሊያሰጋቸው የሚችል ሰው ባይሆንም እንኳን ለሆድ የማይደለል ተቃዋሚ ወይም

ጋዜጠኛ ባጋጠማቸው ቁጥር በመጀመሪያ ማስፈራራትና ማሰር፣ ካልሆነም መግደል ለአስርተ-አመታት የተካኑበት አሳዛኝ

ድራማ ነው። እናም በኢትዮጵያ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ በውሸት ፖለቲካዊ ክስ ተፈርዶባቸው የሚማቅቁ

ኢትዮጵያውያንን ማዕካላዊ፣ ቂሊንጦ፣ ዝዋይ፣ ሸዋሮቢት፣ እና ስማቸው የማይታወቁት የጨለማ እስርቤቶች

ይቁጠሯቸው! እንግዲህ ምርጫ በመጣ ቁጥር ተቃዋሚዎችን እያደኑ ማሰር ምርጫው ካለፈ በኋላ እንደገና መልሶ

መፍታት የተነቃበት የህወሃት ታክቲክ ከሆነ ሰነባብቷል። ስለዚህ መቀየር ያለበት የህወሃት ሶፍትዌር ነው። አርጅቷል።

በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት የዘረኝነት፣ የአምባገነንነት፣ የማን አለብኝ ባይነት፣ አድሏዊና የቂመኝነት አስተሳሰብ ይዞ

አገርን የሚያክል ግዙፍ ነገር መምራት አይቻልም። ስለሆነም በአዲስ አሰተሳሰብ መቀየር አለበት። ከአርባ አመት ከፊት

በነበረ ሶፍትዌር አሁንም አገር እየመሩ ያሉ ቡድኖች መፍረስ አለባቸው። ያ የሚሆነ ደግሞ የህወሃት ዘረኞችን ከስልጣን

በማባረር ነው። ትግል መደረግ ያለበት ከሻቢያ ወይም ከግንቦት ሰባት ጋር አይደለም ፣ ከወያኔ ጋር ነው። ወያኔ

ከተለወጠ ዘላቂ ሰላም ያመጣል፣ የሚገደል፣ በውሸት ክስ የሚታሰር አይኖርም። ከሁሉም በላይ ውሸት የሚፈበርክ

ተቋም አይኖርም።

ነጻነታችን በእጃችን ነው፣ ህወሃት ካልተገረሰሰ እርሐቡም፣ እስሩም ይቀጥላል!

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

4 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

ተነስ ወገኔ Merry Adnen Abdo Frankfurt, Germany

ኣትነሳም ወይ ኣትነሳም ወይ ይሄ

ባንዲራ ያንተ ኣይደለም ወይ?

ከነኩት የማይተው ቆራጥ ህዝብ

ኣንዴ ከተነሳ የሚያስቆመው

የለምና የወያኔ መንግስት እራሱ

በመላው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ዱላ

ይዞ ህዝብን ሲደበድብ ዋለ። ቆይ

ግን ህዝብ ለዳቦና ለዘይት ብቻ

ነው እንዴ ሰልፍ የተፈቀደለት

ኢትዮጵያ ውስጥ?ያሳፍራል።

በጣም ያሳፍራል። ኢቲቪ የሟች

ቤተሰብን ሳያሳየን እናጣራለን ባለ

ቅጽበት ኣልጀዚራ የሟች

ቤተሰቦችን በቴሌቪዥን መስኮት

ብቅ ኣደረገ። ከዚያ ቀጠል

ኣደረገና የወያኔ ኣጎብጓቢ ሰልፍ

በሰላም ተጠናቀቀ ሲል ያ

የለመደው የኢትቪ ጠላት ሰልፍ

ኣንዴት እንደተጠናቀቀ ግልጽ

በሆነ መረጃ ኣሳየን። ከራሱ ታሪክ

ተሞክሮ መማር ያልቻለው

የኢሃዴግ ስር ኣት በተደጋጋሚ

የሚፈጽማቸው የመብት ጥሰቶች

እና ተቃዉሞን በሃይል ለመፍታት

ስለሚወስደው እርምጃም

ችግርን፣ ቁጣን፣ ተቃዉሞን

ከማባባስ በስተቀር መፍትሄ

ካለመሆኑም በላይ በሰላማዊ

መንገድ የስልጣን ሽግግር

እንዲካሄድ እና የኣመጽና የጦርነት

ኣዙሪት እንዲከስም ጭቆናን

ተቋቁመን የምናደርገው ትግል

ለማኮላሸት መሞከሩ የከፋ ኣደጋ

ኣንዳለው ለማስገንዘብ

እወዳለሁኝ። የህዝብን ጥያቄ

ያለፍርሃት በማንሳት እና

ተቃውሞ በማሰማታችን እየደረሰ

ያለዉን ኣፈናና ድብደባ ችለን

በምናደርገው ትግል ውስጥ ድልን

እንጎናጸፋለን። ኣትነሳም ወይ

ኣትነሳም ወይ ይሄ ባንዲራ ያንተ

ኣይደለም ወይ? ድል ለኢትዮጵያ!

አንድ መሪ ኣላት ተብሎ የምትከበር

አገር Zeweter Woldetsadik Frankfurt, Germany

ዜጎቿ ላይ እንዲህ ኣይነት በደልና

ጭካኔ ሲደርስባቸው እየሰማና

እያየ ዝም የሚል መንግስት ኣለ

ቢባል ግፍ ይሆናል። የወያኔ

መንግስት ምን እየሰራ ነው

ያለው? በስደት ያሉት ዜጎች

ኣይደሉም ። ለኢትዮጵያ

ኢንቨስት ለማድረግ የሚገባዉን

ዲያስፖራ በማለት በደስታ

ይቀበለዋል። ኣገሩ ውጭ

በሚደርስበት ችግር ግን ከጎኑ

የለም። እንዴት መንግስት ያላት

ሃገር ዜጎቿ ላይ እንዲህ ኣይነት

ችግር ሲደርስበት ዝም ይላል።

ከዚህ ቀደም ከኣረብ ኣገር ያ ሁሉ

በደል በዝምታ ኣሁን ደግሞ

በደቡብ ኣፍሪካ የደረሰው ጭካኔና

በደል ኣጅግ በጣም የሚዘገንን

ነው። መጠለያ ያጣ ትውልድ

ባገሩ ለመኖር ለመስራት ያልቻለ

ትውልድ ለነገሩ ወያኔ እራሱ ባገሩ

የሚፈጽመው በደል በሰው ሃገር

ቢደገም ምን ቸገረው? ዝምታው

ይብቃ። እኛ በስደት ያለን

ተጋግዘን ያገራችንን ሰላም፣

ፍቅር፣ ኣንድነት እንመልስ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

በተጭበረበረ የፖለቲካ ሽፋን የህግ የበላይነት ተቀብሯል

Mulugeta Mulat Germany

በተግባር ፍትህን እና መልካም

አስተዳደርን እውን ለማድረግ

በቁርጠኝነት የተነሳ ማንም

የለም::ስርኣቱም በጥቅመኞች

የሚመራ ህዝቡም ላላወጣው ህግ

በዝምታ ተቃውሞውን እየገለጸ

ነው; ፍትህን እና መልካም

አስተዳደርን የሚጥስና

የሚያደናቅፍ የስርኣቱ

ባለሥልጣን፣ ዜጋም ሆነ ግለሰብ፣

በማስረጃ ሲታይና ሲረጋገጥ

ዕርምጃ ለመውሰድ ሕግ ፊት

ለማቅረብ ምንም አይነት የተሰራ

ስራ ካለመኖሩም በላይ በባሰ

መልኩ በይፋ ህጎች ሲደፈጠጡ

እያየን ነው:: ባለሥልጣንም ሆነ

ባለ ሀብት፣ ታዋቂም ይሁን ተራ

ዜጋ፣ ከፈለገው ብሔር ብሔረሰብ

ይምጣ፣ የፈለገውን ሃይማኖት

የሚከተል ይሁን፣ የጾታና የዕድሜ

ልዩነት ሳይኖር ተቃዋሚም ይሁን

ደጋፊ ሁሉም ሕግ ፊት፣ ፍትሕ

ፊት፣ መልካም አስተዳደር ፊት

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

5 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

እኩል መሆኑን አምነን በተግባር

ለማዋል ቁርጠኝነት በፍጹም

የለም::ፍትህ መልካም አስተዳደር

የአገልግሎት አቅርቦት እና ሰላም

ለማግኘት በጃችን ያለውን ነጻነት

ለመቀዳጀት ከትግሉ

ያልተቀላቀላችሁ እንድትቀላቀሉ

ያስፈልጋል።

የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር እጦት መልስ የሚያሻቸው ጉዳዮች

ናቸው Wassihun Tegegn

Germany

ለዘላቂ ልማት እንሰራለን በሚል

ስርኣት ውስጥ የመሰረታዊ

የዲሞክራሲ መብቶች በጊዜያዊነት

መኖር እና እንደመነገጃ መጠቀም

ህዝብን አገለግላለሁ ሳይሆን

አጭበረብራለሁ እንደማለት

ይቆጠራል:: የወያኔ ስርኣት

ባለስልጣናት በፍርሃት ተውጠው

በጠበንጃ ሃይል በሚኖሩባት

በዚች ኢትዮጵያችን የፍትህ እና

የመልካም አስተዳደር ጥያቄ

አሁንም እጅግ መልስ

የሚያሻቸው ጉዳዮች

ናቸው::ዜጎች በሃገራቸው

እንዳይኮሩ በመኖር ደህንነታቸው

ላይ ጥርጣሬ እንዲያሳድሩ

እየተደረገ ስለሆነ ይህ ደሞ ወያኔ

የያዘውን ስልጣን ላለመነጠቅ

የሚሰራው ፖለቲካዊ ደባ ውጤት

መሆኑ እሙን ነው::ህዝቦች ህግ

እየጸደ ህግ እየተሽሞነሞነ እና

እየተብለጨለጨ ቢቀመጥ ምንም

የሚጠቅማቸው ነገር እንደሌለ

መታወቅ ያለበት ሲሆ አንድ

ህዝብ ባላረቀቀ ባልተወያየበት እና

ባላጸደቀው ህግ እየተገዛ ፍትህን

እና መልካም አስተዳደርን እንዴት

ማስፈን ይቻላል??? መተማመን

እና የዜግነት ኩራቱን በሚሰብሩ

ባለስልጣናት እየተሰበረበት ያለ

ህዝብ ፍትህን እና አስተዳደራዊ

እንዲሁም አገልግሎቶችን

በተግባል ለማየት እና ለመጨበጥ

አልቻለም:: ለተበደለና ፍትሕ

ላጣ ዜጋ፣ መልካም አስተዳደር

አጥቶ ለሚንገላታ ዜጋ ፍትሕና

መልካም አስተዳደር እንዲኖር

በአንቀጽ ተደንግጓል እያልን

ብናወራ ዋጋ የለውም::

ሃገራችንን ሃገር እናድርግ

Bikisegn Haileleul Germany

የኢትዮጵያዊያን ጥቁር ሳምንት

ኣስደንጋጭ ክስተቶች በተከታታይ

የሰማንባቸው ሳምንታት ሚያዚያ

2007 ኣ\ም። በሊቢያ ከሰው

ያልተፈጠረ በሚመስሉ ነፍስ በላ

ኣረመኔዎች ኣይሲስ የተባለ ኣሸባሪ

ቡድን የኢትዮጵያዊያን

ወንድሞቻችንን ኣንገት

ቆርጠዋል። በጥይት ደብድበዋል።

በደቡብ ኣፍሪካ እስከ

ህይወታቸው የተቃጠሉ በድብደባ

ጉዳት የደረሰባቸው እና

ንብረታቸዉን የተዘረፉ እህት

ወንድሞቻችን፣ በየመን በጦርነት

ቀጠና በስደት ላይ ዘረፋ ብዙ

እንግልት ኣየደረሰባቸው የሚገኙ

እና ኣንዲሁ በሊቢያ በኣሸባሪ

ቡድኖች እጅ ውስጥ ያለበቂ እህል

እና ዉሃ ታፍነው እና ተደብቀው

የነበሩ ኢትዮጵያዊያን

በሃገር ቤት ይኸን ክስተት

መቋቋም ኣቅቷቸው ከኣምሮ በላይ

ቢሆንባቸው መንግስት ለዜጎች

የሚሰጠው ክብር ኣዚህ ግባ

የሚባል ኣልሆን ሲላቸው ብሎም

እኔ መንግስታችሁ ነኝ ብሎ ራሱን

ከሚጠራ ኣካል የማይጠበቅ

ሲሆን ዜጋው በራሱ ተነሳሽነት

ስሜቱን ለመግለጽ ኣደባባይ

ሲወጣ የተለመደው እስር፣

ድብደባና ኣፈና ተስፋፍቶ

ቀጥሏል። ይሄ ክስተት

ኢትዮጵያዊ የሆነን ሁሉ ያለምንም

ልዩነት የሚያስደነግጥ፣

የሚያሳዝን የሚያስቆጭ እና ጥያቄ

የሚያስነሳ ነው። ነገር ግን

የኢትዮጵያ ባለስልጣናት እና

የሃይማኖት መሪዎች ነን የሚሉትን

ባለስልጣናት ስሜት ሊሰጣቸው

ኣልቻለም። ሌላው ኣነዚህ ሃገር

እናስተዳድራለን የሚሉ ሃገር

ኣጥፊ ቡድኖች በትእቢት

በማናለብኝነት እና በንቀት

ሰባዊነት የሚጎድለዉን ተራ

ምላሾቻቸው ለዜጎቻቸው

ሰጥተዋል። ይሄ ምላሻቸው

ኣንደወትሮው ዜጋው ዝም ብሎ

የሚያዳምጠው ኣልነበረም።

የህብረተሰቡን ስሜት የጎዳ እና

በራሱ ተነሳሽነት ወደ ኣደባባይ

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

6 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

በመውጣት ቁጣውን፣

ተቃውሞውን ገልጿል።የወያኔ

ባለስልጣናት ኣሁን ከዚህ ድርጊት

ባለመማር እጃቸውን ወደ ሰማያዊ

ፓርቲ ቀስረዋል። ይኸን ኣመጽ

የሚያደራጁት የጥፋት ሃይሎች

ናቸው ይላሉ። በኔ ኣመለካከት

ኣዎ ህብረተሰቡ ወደ ኣደባባይ

ለብሶት የወጣው በጥፋት ሃይሎች

ምልሽ እና ድርጊት ምክንያት

ነው። የጥፋት ሃይሉም እራሱ

ኣገር ኣስተዳድራለሁ የሚለው

የወያኔ ቡድን ነው። ወያኔወች

ለሃገር፣ ለዜጋ፣ የማይጨነቁ

የራሳቸው ኪስ በመሙላት ስራ

ላይ የተጠመዱ ናቸው። ኪሳቸው

ሞልቶ ከህብረተሰቡ ተከሻ ላይ

ለመውረድ እንደሚያስቡ ግልጽ

ኣይደለም። በነገራችን ላይ የነዚህ

የኢትዮጵያዊያን ስደት በዋናነት

በማን በምን ምክንያት ነው?

የኢትዮጵያዊያን በየደረስንበት

በይ\ኣለንበት ቦታ መገደል፣

መቃጠል፣መንገላታት፣መደብደብ

፣መዘረፍ እና መዋረድ

ለምን?እስከመቼ ነው

የሚቀጥለው ? ችኤ ነው

የሚቆመው?በኔ በግሌ

ኣመለካከት ይሄ የሚሆነው

ሃገራችንን ሃገር ስናደርግ፣ ለወገኑ

ለሃገሩ የሚጨነቅ በትእቢት፣

በማናለብኝነት፣ በንቀት ያልተሞሉ

ሃገር ኣስተዳዳሪወች መፈጠር

ሲችሉ ብቻ ነው። ሃገራችን ሃገር

እንድናደርግ ኣስከመቼ በሰው

ሃገር በስደት እንኖራለን? ወንድም

ኣህቶቼ ጊዜው ኣሁን

ነውልዩነታችንን ወደ ጎን

በማድረግ ኣንድ በመሆን

ሃገራችንን ሃገር እናድርግ።

ለኢትዮጵያ ሃገራችን እና

ለኢትዮጵያዊያን በሙሉ ኣምላክ

በቃችሁ ይበለን። ሰላም።

የ 2007 ምርጫ ቢቀርስ

Emebet Teshome Eschenburg, Germany

በኢትዮዽያ ምርጫ ባይኖርስ

በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ

የሀገር ሀብት ና የሰው ሃይል

የባከነበት ምርጫ

ለኢትዮዽያውያን ሞት፣ ስቃይ፣

ስደት የሚመጣ ከሆነ ቢቀርስ?

ከምርጫው ጋር በተያያዘ

በኦሮሚያ ክልል ና በ አማራ ክልል

የምርጫ ታዛቢዮች በመንግስት

ታጣቂውች እየተገደሉ ነው።

የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትም

ዕንዲሁ ዕየታሰሩ ና ዕየተገደሉ

ነው።በየቦታው ታዛቢወች

በሚደርስባቸው ድብደባ ና ወከባ

ቀየ መንደራቸውን ትተው

ዕየተሰደዱ ነው። ዕናም ምርጫው

ቢቀርስ? አወ ዕወነት ነው የህግ

የበላይነት ዕስጊረጋግጥ ና

ዕውነተኛ ዲሞክራሲ በአገራችን

ዕስኪሰፍን ድረስ ምርጫ

በኢትዮዽያ አሁን ባለው ስርአት

በጭራሽ አያስፈልግም። ለምን?

የንጹሀን ደም ለምን በከንቱ

ይፈሳል?

የአማራን ዘር የማጥፋት ዘመቻ Mengesha Gebru

Marburg, Germany

ኢትዮጵያ የሶስት ሽ አመት ዘመን

ሀገርነት ተክዶ በብሄር ብሄረሰቦች

ዕስር ቤትነት የተተካበት፣ አማራ

የተሰኘ አንድ ትልቅ ኢትዮዽያዊ

ማህበረሰብ በወራሪነት፣

በጨፍጫፊነት፣ በቅኝ ገዥነት

ተወንጅሎ የጎሳ ብሄረሰቦች

የጥላቻ ማራገፊያ ና የተደራራቢ

ቅጣት ሰለባ የተደረገበት

የኢትዮጵያ አባቶች አኩሪ ታሪክ ና

ገድል በፊውዳል ጉልተኛ ስርአት

የጭቆናና የብዝበዛ ተራኪነት

የተለወጠበት የነጻነት ወዳድነት፣

ጠንካራ በራስ መተማመን ና

ብሄራዊ ስሜት ተመልሶ ሊታደስ

በማችልበት መልኩ ከስሩ ተንቅሎ

ዕንዲጠፋ የተደረገበት የሀገራችን

ምሰሶ የሆነው ባህል፣ ወግ ና

ዕምነታችን ባስነዋሪነት፣

ባአድሃሪነት ና ኋላቀርነት

ተፈርጀው ዕንዲዋረዱ፣ ዕንዲጠፉ

የተዘመተበት። ባጠቃላይ

ኢትዮጵያ ና ኢትዮጵያዊነት

አውዳሚ ብሄርብ ሄረሰብ

ከፋፋይ ህዝቦችን ለስደት፣

ለድህነት የዳረገ መንግስት

ስለዚህም ይህ ትውልድ ለራሱ

ክብር ና ለሀገሩ ክብር ሲል ይህን

አምባገነን መንግስት ተባብሮ

ነቅሎ መጣል ነው።

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

7 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

ማስመሰል ይብቃን Molalsh Getnet

Oberusel Germany

ዕኛ ኢትዮዽያውያን ለ24 አመት

በስደት ና በጭቆና ኑረናል። ሰው

በሀገሩ ሰርቶ መኖር ዕየቻለ አገሩን

ትቶ በየብስ በባህሩ ብሎም

ለእስር ና ለሞት ሲሰቃይ

የሚኖረው በጣም ብዙ

ኢትዮዽያዊ ነው። ኢትዮዽያ

ያላት ዲሞክራሲያዊ መንግስት

ነው የሚባለው ከ አፍ ወደ አንገት

የሚያልፍ ነገር ነው። አንድ ሰው

በዲሞክራሲ የሚኖረው ሲባል

ህሳቡን በነጻነት ሲያንጸባርቅ ፣

ሃይማኖት፣ ባህል፣ ደንበር፣ ጎጥ

ሳይወስነው ሲኖር ብቻ ነው።

የወያኔ መንግስት በዘመድ

አዝማድ ተንተርሶ የሚሰራ

ድርጅት ነው። በኢትዮዽያ 2007

ምርጫ የተካሄደው ምርጫ

ሳይሆን ዕርግጫ ነው።

የወገኖቻችን ሞት አብዝቶ

አሳዝኖናል ና በ አደባባይ ማልቀስ

አለብን ብሎ የወጣ ሰላማዊ ህዝብ

ላይ ዱላ የሚሰነዝር አስለቃሽ ጋዝ

የሚረጭ ፖሊስ በተሰማራባት

አገር መኖር ሲሰለቸው ሲሰደድ

ማን ይጠይቀው? ከንግዲህ በኋላ

ግን ማስመሰል ይብቃን። ዕኛ

ኢትዮዽያዊ ለኢ ዲሞክራሲያዊ

የሚመራውን ወያኔን ዕጅ ለዕጅ

ተያይዘን ቀደምቷን

ኢትዮዽያችንን መመለስ አለብን።

በወያኔ ድንክየ የፖለቲካ አስተሳሰብ

ዕስከመቸ? Tilahun Tadese

Borken, German y

ድንክየ አስተሰኣሰብ ግላቸው

የሚመራው ህዋት ኢህ አዴግ

በኢትዮዽያ ህዝብ ላይ ከቀን ወደ

ቀን የሚያደርሰው ግፍ ና መከራ

ልጓም ሊበጅላት ይገባል።

ከሰሞኑ በኢትዮዽያውያን ላይ

በተለያዩ ሀገራት የሚደርስብንን

ስቃይ ና በደል ስናስብ የበደሉ

ዋነኛ መንስኤ የብልሹ አስተዳደር

ውጤት መሆኑ ጸሀይ የሞቀው

ሀቅ ነው። ምክንያቱም ዜጎች በገዛ

ሀገራቸው ላይ ያለምንም አድልወ

በነጻነት የመስራት ና ሀብት

የማፍራት ምኞታቸው በዘመነ

ኢሀዲግ የማይታሰብ ሆኗል።

ይህንንም ብዙወች አደባባይ

ወጥተው ተቃውመዋል። በዚህም

ምክንያት የኢትዮዽያውያ ህዝብ

በዚሁ በተጠላ ስርአት ታስሯል፣

ተገርፏል፣ ተሰዷል፣ ተበድሏል፣

ንብረቱ ተዘርፏል፣ ተፈናቅሏል።

በሌላም በኩል በ በአዋቀሩት

የአፈና ስር አት አማካኝነት

ስራቸውን የሚቃወሙት ሁሉ

ጥቃት ዕየፈጸሙበት ያሉ

መሆኑን ከዚህም የተነሳ ብዙ

ህዝብ ለስደት ዕየተዳረገ መሆኑ

ዕጅግ አሳሳቢ ጉዳይ ነው።

አሁንም በየመን፣ በሳኡዲአረቢያ፣

በደቡብ አፍሪካ ዕንዲሁም

በሊብያ የወገኖቻችን አንገት

ዕንደበግ ዕየተቀላ ወደ ወንዝ

ዕንዲጣል ያደረገው የወያኔ

አስነዋሪ ና አምበገነናዊ የ አገዛዝ

ስልት ነው። ስር አቱም ለዜጎች

ደንታ ዕንደሌለው

የሚያስታውቀው ISIS

በተባለው ሰው በላ የ አረመኔወች

ቡድን የታረዱ ኢትዮዽያዊ

ወገኖቻችን ዕንዲሁም ደግሞ

አንገታቸው ላይ ጎማ ዕየተደረገ

አደባባይ ላይ የተቃጠሉ

ወንድሞቻቸውን ምስል በመያዝ

ድርጊቱን ለመቃወም በወጡ

ንጹሀን ዜጎች ላይ መንግስት

ከጽንፈኛው ቡድን ባልተናነሰ

የከፋ ዕርምጃ ወስዶባቸዋል።

አሁን ያለው የወያኔ ስር አት

ህዝቡን ለከፍተኛ ችግር ና መከራ

ዕየዳረገው ከመምጣቱም በላይ

ህዝቡ በዚህ አስከፊ ስር አት ላይ

ጥላቻውን በከፍተኛ ሁኔታ ዕያሳየ

ይገኛል።ለዚህም ያለመተባበራችን

ከፍተኛ አስተዋጾ አበርክቷል። በኛ

ሀገር ሁኔታ ከህዝብ ጥቅም ይልቅ

የራሳቸውን ና የዘመዶቻቸውን

ሆድ በመንግስት ላይ በሚገኙ

ድንክየ አስተሳሰብ ባላቸው

የፖለቲካ መሪወች ሰበብ በህዝብ

ላይ በዲሞክራሲ ስም

ተቀልዷል፣ተነግዷል፣ ይባስ

ብሎም በሀገሪቱ ላይ ና በህዝብ ላ

ተቅልዶበታል። ስለሆነም የወያኔ

ሹማምንቶች የበላይ ይሚሆኑበት

ዘመን አብቅቶ ኢትዮዽያዊ

አንድነት ዕንዲያብብ ና የህዝብ

የመከራ ዘመን ዕንዲያጥር

የተበታተነውን ና የላላውን ትግል

ይህንን አፋኝ ስራት ለምጣል

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

8 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

በሚስችል መልኩ የተደራጀ

ሀይል በበቂ ሁኔታ አዘጋጅተን

ደካማ የሆነውን የህዝቡን

ዕንቅስቃሴ በማንቃት በሁሉም

የፖለቲካ ድርጅቶች ሆነ መሪወች

በ አንድነት በመቆም ዕስከዛሬ

ድረስ ለውጥ ያላመጣውን

የተናጥል ዕንቅስቃሴ አስወግደን

ህውሀት መራሹ ወያኔን በተባበረ

ክንዳችን ለመጣል ቆርጠን ዕነነሳ።

ድል ለኢትዮዽያ ህዝብ። በግፍ

የተጨፈጨፉትን ወገኖቻችንን

ነብስ ይማር።

የወያኔ ጥላቻ ፍሬ Zafu Amare

Hattersheim, Germany

ወያኔ ለትግራይ ህዝብ ሀብትና

ብልጽግና አመጣ ብለው

የሚያምኑ ሰወች ብዙ ናቸው።

ወያኔ የስልጣን ወንበሩ ላይ

በመውጣቱ ትግሬወች ሁሉ

አልፎላቸዋል። ይታመናል በተለይ

በ አውሮፓ ና በ አሜሪካ የሚኖሩ

ኢትዮዽያውያን በዚህ ላይ

የጠነከረ ዕምነት አላቸው። በዚህ

ጉዳይ ላይ ከኢትዮዽያ ውጭ

ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ

ይደረጋል። በኢትዮዽያ ውስጥ

ግን የተፈራ ርዕስ ነው። ውስጥ

ውስጡን ዕንጅ አደባባይ

ለማውጣት ጊዜው የደረሰ

ይመስለኛል። አረጋዊ ብርሄ፣

ገብረ መድህን አርአያ፣ አሰግድ

ገብረ ስላሴ፣ አብርሀ ደስታ

ዕየደጋገሙ ቢያነሱትም ሌሎች

በቁም ነገር የተቀበሉት

አይምስሉም። ህዝቡ ግን በራሱ

መንገድ ዕየተናገረ ና ምስክርነት

ዕየሰጠ ነው። በመቀሌ

የተሰራውን የመኳንንት መንደር

ህዝቡ ´´አፓርታይድ´´ ብሎ

ሲሰይመው በ አዲስ አባ ባ

የተሰራውን መንደር ´´መቀሌ´´

ብሎ ሲሰይመው ዕየመሰከረ

ነው።

ያለፈውን ስርዓት መናፈቅ

ዮሐንስ ደሳለኝ Frankfurt, Germany

አንዳንዴ የአገራችንን የፖለቲካ፣የማህበራዊና

የኢኮኖሚ አዘዋወር ሳስበው ግርም ይለኛል በተለይ በአሁኑ ግዜ ብዙ ሰዎች ያለፉትን

ስርዓቶችን መመኘት ጀምረዋ። ይህ ለእኔ እንደ አንድ ኢትዬጵያዊ ጤናማ አመለካከት አይመስለኝም፣ ለወያኔ ግን እመራዋለሁ በሚለው ህዝብ ዉስጥ እያስቀመጠ ያለውን ስነ ልቦና ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ያለፉት ሁለቱም ስርዓቶች የራሳቸው የሆነ ጥፋትም ልማትም አስተናግደዋል ፣ ከትክክለኛ ግንዛቤና ስሜታዊ ባልሆነ ምልከታ ስናየው ግን ሁለቱም ሥርዓቶች ይሄን ያህል የሚናፈቁ አልነበሩም ግን ሆነ ፣አዎ አንድ ህዝብ ትክክለኛ መስመር አቅጣጫና የማንነቱን ታሪክ

የሚያወሳውና የሚያሳየው ሲያጣ

አማራጭ ባይሆንም ላይመለሱ የሄዱትን መናፈቅ ግድ

ይለዋል። አሁን ነዉ እንግዲህ ጎልያዶቹ መሪዎቻችን ራሳቸዉን ማየት ያለባቸው፥ ይህ ወቅት

ነገሮችን አመላካችና ወያኔም በምን ምክኒያት ነው ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ሙሉ የህዝብ ይሁንታ ማግኘት ያልቻልኩት ብሎ መጠየቅ ያለበት። ለእኔ እስገሚገባኝ ድረስ የአሁኖቹ መሪዎቻችን ህዝብ ያልተቀበላቸው ምክኒያቶች ዘርፈ ብዙ ቢሆኑም ዋናዉ ግን የወያኔዎቹ ኢትዬጵያ ለምትባለው

አገር ደንታ ቢስነት ነዉ ፣ ኤርትራን ከማስገንጠል የጀመረዉ ሀሳብ ዛሬ በየቦታዉ ተዳርሶ ያች አንድነቷን ለረዥም ግዜ ጠብቃ የቆየች አገር ተመልሳ አፄ ቴዎድሮስ ከመንገሳቸው በፊት

ወደነበረዉ ዘመነ መሳፍንታዊ አገዛዝ ወስጥ የተዘፈቀችዉ፡ የአማራው ገዠ ነኝ የሚለው የሚያስተዳድረውን አማራን ይሳደባል የኦሮሚያ አስተዳደር የኦሮሞ ወጣቶች ፍትሃዊ የሆነ የመሬት ክፍፍል ይኑር ዴሞክራሲያዊ የሆነ አሰራር

ይስፈን ብለው በጠየቁ

የአስተዳደሩ መልስ የጥይት አረር ሆነ ፧ የትግራይ ልጆች በስማቸው ሲነገድ የበይ ተመልካች ሆነው ከሌላው ወንድሞቻቸው ለማጣላት ሴራ ሲጠነሰስባቸው አቅም አጥተው ተቀምጠዋል።ታዲያ ይህ ሕዝብ ተገነባ የተባለው መንገድ፡ ተዘረጋ የተባለው የባቡር መስመር ፡በህንጻ ሜካፕ የተዥጎረጎረችው አሮጊቷ አዲስ አበባ ልቡ ውስጥእንዴት ይግቡና ይዋጥለት። ተወደደም ተጠላም እኛ ኢትዬጵያዊያን ስናድግ በተረት ፡ በታሪክ ትምህርት

አሊያም በተለያየ ጊዜና ሰዓት የአገራችንን ታላቅነት ፡የአፍሪካ

ህዝብ ነፃነት ተምሳሌትነትና አንድነቷን ጠብቃ የቆየች መሆኗ ተነግሮናል አምነንም በውስጣችን

አትመነዋል እንጅ እንደ አሁኑ ገዥዎቻችን የተለየ የምድጃ ዳር ወግ ወይም ተረት አልሰማንም ፣

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

9 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

ለነገሩ እነሱም ከእኛ የተለየ አልሰሙም ነበር የምዕራባዊያን

ብርና ብልጭልጭ ስጦታ በለጠና ተተራምሰው ዙሪያዋን የተቀደደች አገር አበጁልን እንጅ።

ይህ አልበቃ ብሏቸው ዛሬ በእነሱ ግዜ የተፈጠሩት ብላቴናዎች መጻፍ ሲጀምሩና ደባቸውን ሲያጋልጡ ጎልያዶቹ ወያኔዎች ባዶነታቸው በገሃድ ወጣና እንደ አንድ ዜጋ እንጻፍ እንናገር ፡ ዜጎች ቢያንስ የመናገር የማሰብ ነፃነታቸው ይከበር ባሉ ለመስማትም ለመናገርም የሚቀፍ ስቃይና እንግልት እያደረሱባቸው የሚገኙትና በአገሪቷም ላይ የማይረሳ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ እንዲያልፍ የተፈለገው ። ስለዚህ ውድ መሪዎቻችን እስቲ ረጋ በሉ አትዋከቡ የጦር መሳሪያ እንደሆነ ደርግም ይዞት ነበረ አልጠቀመውም እናንተው ራሳችሁ ነጥቃችሁ አብሮ የታገለውን ወገናችሁን ወጋችሁት ። ግን ግን ስታስቡት ይህ የጦር መሳሪያ አገዛዝ ነገ እንደሚያከትምለት ታሪክ አያስተምራችሁም ፤ እርግጠኛ ነኝ ናፖሊዮን ቦናፖርትን ፡አዶልፍ ሂትለርን ፧ የቅርብ ግዜ ሳዳም ሁሴንን፡ ወንድም ጋዳፊን ታውቃላችሁ ብየ እገምታለሁ ፡ወይም ደግሞ ወዳጃችን የአክራሪዎችን ሴራ ድባቅ የመታ ያሉትን ሁስኒ ሙባረክን ስትሬቸር ላይ ሆኖ ፍርዱን ሲከታተል አድናቂዎቹ ምዕራባዊያን ከነመፈጠሩም እንደረሱት። የአሜሪካፕሬዚዳንት እናንተን ለመጐብኘት መምጣት (መቼም ህዝቡን ለመጐብኘት እንዳልመጡ እርግጠኛ ነኝ።) ዴሞክራት መሆናችንን አሳይቷል ብላችሁ ከሆነ አትሸወዱ ግዜው ሲደርስና የአንድነት የዴሞክራሲና የነፃነት ታጋዮች ሲመጡ ከምንም አያስጥሏችሁም ፣ የመንጌ አትመጣም ወይ ፣መንግስት

የሌለው እዚህ ብቻ ነው ፣የውስጥ አንበሳ የውጭ ሬሳና የመሳሰሉትን የህዝብ ብሶቶች ቆም ብላችሁ እያደመጣችሁና ድንጋይ ክመራውን ትታችሁ ቅድሚያ ለሰው ልጅ ደህንነት ስሩ አገር ን መውደድን ተማሩ ፡ በተለይ ደግሞ የያገባኛልና የተጠያቂነት ልምድ አዳብሩ ። የ 1 ለ 5 ፍልስፍና እንደሆነ በአሁኑ ዘመን አይሰራም ሰሜን ኮሪያ ዓይነት አገር መመስረት ፈልጋች ከሆነ ያ ግዜ አልፏል እንደ ኬምልሱንግ ሁሌ ይዘመርለታል ብላችሁ የጠበቃችሁት ሟቹ መሪያችሁን ነበረኝ ካለው ራዕዮ ጋር ህዝቡ ቀብሮት ከስድብና ከዘለፋ እፉይ ብሏል ፡ይባስ ብሎ « አትመጣም ወይ መንጌ አትመጣም ወይ » ዜማን ተቀኘ የጨነቀው እርጉዝ ያገባል እንደሚባለው ህዝቡ ጭንቀቱን ፧ብሶቱን ፧አማራጭ ማጣቱን በግልጽ ነገራችሁ ። የመንጌ አትመጣምን ዜማ በንቀት አትመልከቱት ልብ ያለው ልብ ይበል ውድቀት የሚጀምረው እመራዋለሁ የሚሉትን ህዝብ ሲንቁና ሲጠየፉ ነው ።

የሕወሓት ማፊያ ቡድን ከምድረገጽ መጥፋት

አለበት Mulugeta Teka

Dreieich, Germany

የሕወሓት ማፊያ ቡድን ወራዳ

ነው:: ኢትዮጵያ የምትባል አገር

እንዳትኖር የሚመኝ ይህ አሸባሪ

ድርጅት ለማንም አይበጅም::

ብናወራለት ተተካኩ ተባሉ

ተፋቀሩ ብንልለት ምንም

አይበጅም::የሚበጀን ነገር ቢኖር

ትግሉን በአራቱም አቅጣኛ

በማጠናከር ሕዝቦችን

በማስተባበር በመቀስቀስ እና

በማደራጀት ይህንን ከይሲ

የማፊያ ቡድን ማስወገድ ብቻ

ነው:: እስኪ ራሳችን እንጠይቅ?

ስንቶቻችን ነን ለራሳችን አላማ

እና ግብ ጠላቶች የሆንን?በወሬ

ናዳ እያሽካለልን ትግሉን

የጎተትን?እርስ በራሳችን በተራ

የመንደር ወሬ ተቧድነን

የምንወነጃጀል? ከትግል ይልቅ

በሃሜት እና በፍረጃ ላይ

በፕሮፓጋንዳ ላይ የተተከልን

ስንቶቻችን ነን? ከዚህ አይነቱ

ጋሬጣ ራሳችንን አላቀን ሕዝብን

አስተባብረን የሕወሓትን ጉጅሌ

አገዛዝ በተገኘው መንገድ ሁሉ

በጋራ እና በአንድነት ሆነን

መደምሰስ አለብን ::

አይደለንም::ደግሜ እናገራለሁ

ጠላቶቻችንን የምናንበረክክበት

እና በሚገባቸው ቋንቋ

የምናናግርበት ጊዜ ላይ ነን::

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

መሪ አልባ አገር Sara Mesfin

Viernheim, Germany

ኢትዮጵያ ዛሬ የምትተዳደረዉ

የኢትዮጵያ ሕዝብ ወይስ

በአረመኔዉ የመለስ ዜናዊ ሙት

መንፈስ? ብዙዎች የሚስማሙበት

ግን ራሱን የትግሬ ነፃ አዉጪ ነኝ

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

10 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

ብሎ በሚጠራዉ የዘረኞችና

የነፍሰገዳዮች ገዢ ቡድን መሆኑን

ነው።በእርግጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ

ራሱን እያስተዳደረ እንዳልሆነ

እናዉቃለን። ማንም በዚህ መልኩ

ራሱን እያታለለ

አይገኝም።የኢትዮጵያ ሕዝብ

ራሱን ማስተዳደር ጀምሯል

የሚባለዉ ሃቀኛ ተወካዮችን

መርጦ በእንደራሴና በአደራ

መልክ በአመራሩ መንበር ላይ

ሲያስቀምጥ ብቻ ነዉ። እስከአሁን

ደግሞ ይህ ስላልሆነ በሥልጣን

ላይ ያለዉ የትግሬ ነፃ አዉጪ

ቡድን በዉስጥና በዉጭ ፀረ

ኢትዮጵያ ሃይሎች እየተረዳ

በጉልበት የገባና በጠመንጃ የሚገዛ

ኃይል ነዉ።የኢትዮጵያ ሕዝብ

የሚጨነቀዉ በኢትዮጵያ

የመንግሥት ምስረታ ላይ ነዉ።

የሌሎቹ ጭንቀት ግን

ስለተፅእኖአቸዉ ያስቀመጡት

አሻንጉሊት አገዛዝ መመሪያቸዉን

ከማክበሩ ላይ ነዉ። ይህ

መሠረታዊ አላማና የእምነት

ልዩነት በመካከላችን አለ። ሌላዉ

የሚገርመዉ በሥልጣን ወንበር

ላይ የሚገኘዉ ኃይል ሕልሙና

አላማዉ ስልጣን እንጂ የሕዝብ

ሰላም ስላልሆነ ዛሬም

እንደትናንቱ ከተቃዋሚ ኃይሎች

ጋር አይን ለአይን ለመተያየት

አለመቻሉ ነዉ። በሌላ አገር

ቢሆን ዲሞክራሲ በዚህ የፓለቲካ

ይዘትና ሥርአት ዉስጥ በስም

እንኳ ባልተጠቀሰ ነበር።

ዲሞክራሲ እርስ በርስ መፈራራት

ባልሆነ ነበር። ኢትዮጵያዉያን

ተገናኝተዉ ተወያይተዉና በሃሳብ

ተፋጭተዉ ከአንድ ስምምነት ላይ

ለመድረስ አለመቻል በበለጠ

ሁኔታ ጠላትን ከመጥቀሙ ባሻገር

ታላላቅ መንግሥታቱ በአገሪቱ

ሉአላዊነት ዉስጥ እንዲፈተፍቱ

ማድረጉ ግልፅ ሆኗል። ሥልጣን

የያዙትም ሆነ ተቃዋሚ ሃይሎች

በነፃ ኢትዮጵያዊነት ኩራትና

መንፈስ “በኢትዮጵያ ጉዳይ

የሚያገባን እኛ ብቻ ነን የሌሎችን

አቋም አዉቀናል ስለዚህ የዉጭ

ኃይሎች እጃቸዉን ይሰብስቡ”

ከሚባልበት ደረጃ መድረሳቸዉን

በተረዱ ነበር። የዓላማና የአቋም

ልዩነት መኖሩ የዉጭ ዳኛና

ተቆጭ እንድንሾም አስገድዶናል።

የኢትዮጵያን የዘወትር ተጋድሎ

ጌታ ለመለዋወጥ አልነበረም።

“ኢትዮጵያን ለኢትዮጵያዉያን”

መፈክር በተግባር መተርጎም

ነበረበት። ለኢትዮጵያ ነፃነትና

ሕልዉና የታገሉና የዉደቁ

ልጆችዋ ለአንድ አፍታ ቀና ብለዉ

አገሪቱ ልምድም እዉቀትም

የኢትዮጵያዊነት እምነትም

የሌላቸዉ ጎጠኞች የተንሰራፉባት

መሆኑን ከተረዱ አፅማቸዉ

መቃብራቸዉ ዉስጥ ምንኛ

በተንቀጠቀጠ ነበር ያሰኛል?!

ኑሮ ተወደደ Habetamu Gabermaram

Germany

በእናት ኣገራችን ኢትዮጵያ

ኣሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ የኑሮ

መወደድ ነው። ኣምባገነኑ

የኢትዮጵያ መሪ የኢሃዴግ

መንግስት ስልጣን ላይ ከሰፈረ

ጀምሮ የኑሮ ውድነት ኣየናረ

እንጅ እየቀነሰ ኣይታይም። የዚህ

ችግር ምንጭ የጠንካራው ኣርሶ

ኣደር ገበሬ መሬት በግፍ መነጠቅ

ነው። ከዚያም ገበሬው ያለ ስራ

መቀመጥ ወይም ከቤት ንብረቱ

ከቀየው ያለ ፍላጎቱ በመፈናቀል

ሳይወድ በግድ ወደ ከተማ

በመፍለስ ወደ ምጽዋእት(ልመና)

ስራ ላይ ይሰማራል። <<ለምን

ሰርተህ ኣትበላም ጉልበት

ኣለህ>>በማንልበት ጊዜ መሬቱን

የኢሃዴግ መንግስት ነጥቆኝ ምን

ሰርቼ ልበላ ነው የሚለን

ይታያችሁ። ጉልበት ጤና እያለው

የሃገራችን ህዝብ በልመና

ሲተዳደር በጣም ያሳዝናል ኣርሶ

ኣደሩ ገበሬው ነበር እኮ

የከተማውን ሰው ሆዱ ሞላ ዛሬ

ለሃዱ ሲል እነዚያን ሞፈር ቀንበር

የጨበጠበት እጁን ለልመና

ዘረጋቸው። የከተማን ኑሮ ያላየ

ሁሉም ልስራ በማለት ወደ ከተማ

ይገባል። የስራ እጦት ልመና ላይ

ይጥላል። ወገኔ እስከመቼ ይሆን

የገዥው መንግስት ግፍና ጭካኔ

የሚቀጥለው ። ኑሮ ተወደደ

ከማለት ይልቅ ኑሮ የተወደደበትን

ምክንያት በጋራ በኣንድነት

ታግለን እናጥፋና ገበሬውም

በታየው ኣርሶ የሚተዳደር

ለከተማውም የሚተርፍ እንዲሆን

በኣንድነት እንታገል።

እግዚኣብሄር ሃገራችንን ይባርክ።

ኣሜን።

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

11 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

መሪ የሌለው ህዝብ Rute meleak

Rüsselsheim, Germany

የኢትዮጵያ ህዝብ የተፈጥሮ

እድሉ ሆኖ በህዝብ የተመረጠ

የህዝብ መብት የማያከብሩ

መሪዎች ማግኘት ኣልቻለም።

የተለያዩ መሪዎች እየተፈራረቁ

ሃገሪቱን ሲመሩ ቆይተዋል።

እስካሁን ድረስ ያለው የመንግስት

ስልጣን በጦርነት እና በመሳሪያ

ያሸንፋሉ። ሃይል የሃገሪቱን

የመሪነቱን ስልጣን እየያዘ

ቀጥሏል። ገዥው ወያኔ በመሳሪያ

ሃይል ወደ ስልጣን ከመጣ ሃያ

ኣራት ኣመታት ያስቆጠረ ሲሆን

እነዚህ ጊዜያት ለኢትዮጵያ ህዝብ

የመከራና የሰቆቃ ኣመታት ነበሩ።

ወያኔ በሚከተለው የብሄር

ፖለቲካ ምክንያት ለብዙ ኣመታት

በሰላምና በፍቅር ተቻችሎ ሲኖር

የነበረውን ህዝብ በጎሳና በብሄር

እንዲከፋፈልና ኣንዱ ብሄር

ከሌላው ብሄር ጋር በጥላቻ

እንዲተያይ እያደረጉት ይገኛል።

ከምርጫ 1997 በሁዋላ

የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ወደ

መቃብር የወረደ ሲሆን መንግስት

በተቃዋሚ ፖለቲካ በደረሰበት

ሽንፈት የተለያዩ የዴሞክራሲ

ስራቱን የሚያቀጭጩ ኣፋኝ ህጎች

በማውጣትና ጠንካራ የፖለቲካ

ፓርቲዎች በማዳከምና በማፍረስ

የሃገሪቱን የዴሞክራሲ ስር ኣት

የቁልቁለት እንዲጓዝ ኣድርጓል።

የወያኔ መንግስት በኣሁኑ ወቅት

ጠንካራ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣

ጋዜጠኞችን፣ጦማሪያን፣

የተቃዋሚ ኣባላትንና የሞስሊም

መፍትሄ ኣፈላላጊ ኮሚቴዎችን

ስለ ሃገራቸው ጉዳይ ያገባናል

ስላሉና ፍትህ ስለጠየቁ በገዥው

ፓርቲ የሃሰት ክስ ተከሰው በእስር

እየማቀቁ ይገኛሉ። ኣንዳንዶችም

በገዥው ፓርቲ በሚደርስባቸው

ጫና እስራትና ማስፈራሪያ

ሃገሪቱን ጥለው ለመሰደድ

በቅተዋል።

በዘንድሮ ምርጫ ከምርጫው

በፊት ኣስቀድሞ ገዥው እንዳሸነፈ

የምርጫው ዉጤት የታወቀ

ሲሆን ገዥው ፓርቲ የይስሙላ

ምርጫ በማካሄድና የህዝብን

ድምጽ በመስረቅ መቶ ፐርሰንት

ኣሸነፍኩኝ በማለት የኣለም

ህዝብን በማስገረም ላይ ይገኛል።

በምርጫው ውጤት ኣምባገነን

መሆናቸውንና ለተቃዋሚ

የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃሳብ ቦታ

የሌላቸው መሆኑን

ኣረጋግጠዋል። ገዥው መንግስት

ምርጫ የሚያካሂደው ሌሎች

መንግስታትን ዲሞክራሲያዊ

መንግስት ሆኖ ለመታየት ኣንጅ

ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ኣስቦ

ኣይደለም።

በሃገራቸው መብታቸው የተገፋ

ህዝቦች መብታቸዉን ለማስከበር

እና ነጻነታችውን ለማስመለስና

ሃገሪቱን ካለችበት ውድቀት

ለመታደግ ሃገር ውስጥም ሆነ

በውጭ የሚካሄደው ትግል እስከ

ነጻነት ድረስ ተጠናክሮ

እንዲቀጥል እጠይቃለሁ። ድል

ለኢትዮጵያ ህዝብ።

የነጻነት ተስፋ Soliyana kindie

Frankfurt, Germany

የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን

በትግሉ እንዲቀዳጅ በህብረት

ለመታገል ሁላችንም የኢትዮጵያ

ልጆች በያለንበት እንደራጅ።

ይህንንም ለማለት ያስቻለኝ

ዋናው ጉዳይ ዘረኛውና ኣፋኙ

ህወሃት መራሹ በኢትዮጵያ ህዝብ

ላይ በርካታ ዘግናኝ ወንጀልና ደባ

እየፈጸመ ይገኛል።

ዘረኛው የወያኔ መንግስት

ህዝቦችን ከቀያቸው ከቤት

ንብረታቸው እያፈናቀለ በኦሮሞ

ህዝቦችና በኣማራው ብሄረሰብ

ንብረት እየወረሰ ልግል ባለሃብት

እያደለ ልጆቻቸው ጥሩ

የትምህርት እድል ኣግኝተው

የወደፊት እጣ ፈንታቸውን

በመልካሙ እንዲያዩ ራእያቸው

ድቅድቅ ጨለማ ተላብሷል።

እናት ኣገር ኢትዮጵያ ፍትህ፣

እኩልነት፣ ነጻነት፣ ዴሞክራሲ

የሚጠይቁትን ጦማሪያን

ጋዜጠኞች ዘብጥያ በማጎር

የሃይማኖት እኩልነትን

በሚጠይቁት ሞስሊም

ወንድሞቻችን ላይም ይህ ነው

የማይባል ግፍና በደል እያደረሰ

የከፋ መከራ ገፈቱንም እየወሰደ

ይገኛል። እምቢ ኣሻፈረኝ

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

12 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

የተወለድኩበት ሃገር ነጻነት፣

ኣኩልነት፣ ፍትህ ኣልባ በመሆኑ

ተምሬ ሃገሬንና ወገኔን ቤተሰቤን

ለመርዳት የማልችልበት ደረጃ

ስለደረሰ ወጣቱ ወደ ሰው ሃገር

ስደትን መርጦ በሊቢያ በረሃ

ኣንገቱ በኣክራሪ ሞስሊም

ጽንፈኞች እየተቀላ

በሜዲትራኒያን ባህር ኣየሰጠመ

ሴቶች እህቶቻችን በየኣረብ ኣገሩ

እራሳቸውን ከፎቅ በመጣል

ወይም ህይወታቸውን በራሳቸው

በማጥፋት እንደ ኣማራጭ

ኣድርገው ይዘውታል። ይህ ሁሉ

ይህን ሁሉ ሰቆቃና ግፍ ያመጣው

የወያኔ የግፍ ኣገዛዝ ነው። እናት

ኣገር ኢትዮጵያ የፋሽሽት

ኣምባገነናዊ ወንጀል ሳቢያ

ክብሯን ነጻነቷን ሰብ ኣዊ

መብቷን ኣጥታ መብት፣ ክብር፣

ነጻነት ኣጥተው በወያኔ ፍርፋሪ

ሆዳቸዉ ባበጠው ካድሪዎች

እየተረገጡና እየተገረፉ የሰቆቃ

ህይወታቸውን በቃሊቲ ወህኒ

ቤት እየኖሩ ይገኛሉ።

ባጭሩ ከላይ እንደዘረዘርኩት

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገው

ግፍና በደል ሳያበቃ የወያኔ

መራሹ መንግስት በ 2007 ኣ\ም

የመንግስት ምርጫ

በዴሞክራሲያዊ ምርጫ መቶ

በመቶ ኣሸንፊያለሁ በማለት

ዴሞክራሲያዊ መንግስት ሆኖ

ቀርቦልናል። ቁርጠኛ የህዝብ ልጅ

የሆነውንም ግንቦት ሰባት ዋና

ጸሃፊ ኣንዳርጋቸው ጽጌ

በሽብርተኝነት ፈርጆ እያለ የወያኔ

መንግስት የውጭ ጉዳይ

ሚኒስትር ቴዎድሮስ ኣድሃኖም

እስረናውን ኣንዳርጋቸው ጽጌን

በጥሩ ሁኔታ እንደተያዘና ፍጹም

የሆነ ዴሞክራሲ የሰፈነባት

ኢትዮጵያ ኣድገው

ኣቅርበውልናል።ቆንጆ የውሸት

ድራማ ሰሚ ቢያገኝ። ውድ

ወገኖቼ በኢትዮጵያ

ዴሞክራሲያዊ የሆነ በህዝብ

የተመረጠ መንግስት ለመመስረት

የዘር፣ የሃይማኖት ልዩነት

ሳይኖረን በጋራ የተባበረ

ድምጻችንን ለኣለም ኣቀፍ

ህብረተሰብ በማሳወቅ ለኣንዴና

ለመጨረሻ ጊዜ የህወሃትን

ኣፓርታይድ ለማስወገድ

በቁርጠኝነት እንታገል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን፣

ክብሩን ለመጎናጸፍ ከወጣት

ኣርበኞች ወንድሞቻችንና

እህቶቻችን ጋር ወደ ጦር

ኣውድማ ሜዳ በመቀላቀል

ኢትዮጵያዊ ግዴታችንን በትጥቅ

ትግል እንተርጉም። ድል ለሰፊው

ህዝብ።

ኢትዮጵያን እግዚኣብሄር ይጠብቅ።

Ethiopia is Stuck Samuel Petros

Alsbach, Germany

In 180 degree turn around

from ist previous

laudatory positions, the

economist concluded a

highly critical article as

follows- <<endless red

tape and restrictions on

finance deter

investors…only further

reforms can sustain the

goals of economic growth

and political

stability…(but) Ethiopia

is stuck.>>

Reform versus deadlock:

That is the heart of the

economic problem. First

in the dock is the EPRDF.

It has turned the entire

state and its components

in to a satellite. Front and

state have merged. Civil

servants who are are not

party members are few

and far between. As a

result the agenda of the

front and its hierarchy

takes precedence over that

of the state, party

obedience hinders the free

exercise of professional

competence. The

complaints about this

issue are constant. Yet the

smarter public

management required by

a more advanced

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

13 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

economy demands that

administrative managers

should have freedom in

their analyses and

proposals. In the private

sector, the obligation to

meeting the government.

The youth of

Ethiopia

Mulatua Ayehu Fanta Aschaffenburg,

Germany

A great deal has been said

about the youth of

Ethiopia being the

countr,s next generation

of leaders in the Ethiopian

political scene, however,

the youth are mainly

sought not as leaders but

rather as side kickers to

the establishment.

One of the most tasks of

families, the society and

the government is to

educate and empower the

youth but do these entities

genuinely dialogue and

have a common

understanding on this

mission? Are they

committed to transform

the youth from meek

followers to leaders? Not

by a long shot! They do

not go much beyond

engaging in empty

rhetoric. Being committed

to enable the youth

requires ensuring that

they participate directly in

the political economic and

social affairs of their

country. if one were to

ask what meaningful steps

have been taken to

enhance the youth,s

capacity and bring them

to leadership positions,

the sad answer is

practically nothing. This

obviously does not bode

well for the country.

The youth in Ethiopia are

surrounded by a raft of

problems. The number of

establishments where they

do both mild and hard

drugs, imbibe alcohol and

resort other vices close to

dwellings schools and the

work place is mush

rooming by the day. a

sizable proportion of

young graduates who

have joined the work

force barely make it day

to day owing to the

inadequate salary they

draw. Uneven greater

number is unemployed

and a burden to their

families. Unless a

comprehensive policy is

formulated to extricate the

youth from such multi-

faceted challenges and

prepare them to take over

the leadership of their

country, the ensuring

consequences will very

much be dire.

Are political parties

making tangible efforts to

enable the youth beyond

recruiting them to swell

their membership and use

them as slogan material?

Have they ever made a

conscious decision to

abandon the common

practice of employing the

use to do legwork and

elevate them to positions

of responsibility? Do they

adequately steep youth in

their ideology and coach

them on leadership or do

they imbue them with the

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

14 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

politics of intolerance as

they inclined to? Do they

embrance or shun

youngsters who are

critical thinkers self-

starters and display

leadership quality? All

political parties Ethiopia

including the ruling

Ethiopian peoples

revolutionary democratic

front (EPRDF) are guilty

of not giving the due

attention the youth

deserve.

Ethnic politics is

an existential

threat to all

Ethiopians

Desalegne Abebew & Yalemwork Meswaet Schöneck, Germany

It is not an accident that

after almost 25 years of

hate mongering you now

have a generation of

Ethiopians who are as

alien to each other as they

are to foreigners. Without

a forward looking

national forgiveness and

reconciliation strategy and

a shared history built on

interaction and common

experience, ethnic groups

are wider apart today than

before, and as a result, the

very fabric of the nation is

withering away. You

can’t cultivate suspicion

and hate at the primary

and secondary school

levels and suddenly

expect harmony to swell

at the university level.

Moreover, you can’t

aspire to achieve peace,

stability, and sustainable

economic progress in

such a poisonous

environment. No amount

of “renaissance” or

“growth and

transformation plan”

would get you there. Any

progress made in such a

divisive environment can

only be fleeting. First you

need to shrink the

yawning and ever-

expanding gap among

ethnic groups. In fact, if

not corrected quickly, the

divide and discord will

eventually lead to assured

conflict and

disintegration. Ethiopians

need to heed Obama’s

July 26th message to

Kenyans – “that a politics

that is solely based on

tribe and ethnicity is a

politics that’s doomed to

tear a country apart. It is

a failure – a failure of

imagination.”

How is it possible to hold

an election in a diverse

and huge country such as

Ethiopia and come out

winning 100 percent?

This defies elementary

logic, decency, and self-

respect. You can’t have it

both ways. You either

declare no elections and

rule by fiat or conduct

elections and accept the

verdict of the people (no

contradiction in both

instances).

One needs to also

remember that the TPLF

and its lackeys, after

nearly 25 years of

unaccountable leadership,

have amassed

considerable wealth and

influence that they want

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

15 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

to protect. But in an

environment of ethnic

disharmony, ethnic

favoritism

(discrimination), growing

income inequality and

poverty, and lack of

freedom and liberty,

sustaining the status quo

is increasingly becoming

difficult. Such is the state

of the TPLF today that

something has to change;

otherwise the cancer of

ethnic politics could have

a Frankenstein ending,

consuming its very

creator, the TPLF.

Ethiopia is where it is

now after sustained

propaganda, misguided

decisions and actions

made by those in power

for nearly the past 25

years. It will take time,

effort and resources to

reverse the damage

already inflicted.

It is this generation’s

historic calling to devise a

more promising and

brighter future based on

love and respect for each

other and individual

freedom and liberty for

all.

The Future is indeed in

our collective hands!

God Bless Ethiopia and

Ethiopians!

What shall we do?

Hailu Kassa (Niedernhausen,

Germany)

Democracy is first

originated from God that

no one else has the right

to give and to take. It is

just naturally gifted from

God. But human beings

limited this right from

exercise. That is what we

see every day in many

African Countries

especially east Africa

particularly Ethiopia.The

current government of

Ethiopia has been on

power since May 1991

throwned after civil war

with the former regime

Mengistu Hailemariam

(Derg). The EPRDF first

started this war fooling

the Ethiopian People that

it brings democracy and

freedom but it was

andisironic.Rather this

regime is killing the

Ethiopian people

especially youth mentally,

physically, and spiritually

through the name of

Pseudo-Democracy

running a strategy of

cheating the International

Communities as if there is

democracy and freedom

in the country but the

truth is does not care

locally for its people. That

is what the Europeans and

American do not know.

What shall we do!!!

Every Five year there is

the so called election

organized in Ethiopia but

itisandhasneverbeenfreean

d fair.Againitis a

systemtocheatthe western

nation as if there is

democratically elected

government but the truth

is not never has been. At

first the election board is

supposed to be neutral but

internally it is set up by

EPRDF and its stuff

members. They are all

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

16 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

hidden supporters of the

current government. It is a

fact that no strong

opposition political

parties in the country

because of the different

systematic attack by the

government in different

times many of them left

the country and some

others are in Jail. There is

also limited air time of

electronic media for

opposition political

parties. Much of it used

by the government for its

propaganda. Every civil

servants are forced to

elect EPRDF directly and

indirectly.The Ethiopian

people are desperate on

election because they

always know beforehand

how in the election. The

people do not have trust

on the government but in

timidated to participate in

this foolish election. Over

all there is no and has

never been free and fair

election in Ethiopia.

What shall we do!!!

Medias are all

monopolized by the

government. There are

some private printmedi as

but they are always under

the pressure of this

government. Most of the

private media institutions

are attacked by the

government, the flow of

Journalists out of Ethiopia

is increasing from time to

time. A number of

Journalists and bloggers

are now found in jail. If a

Journalist and Media

organization witness the

truth on the government

poor quality and they are

claimed as Terrorist.

EPRDF always dislike

criticism. So if its own

people do not witness the

truth, whoelsewitness.

What shall we do!!!

Every year in Ethiopia

more than hundred

thousand students

getgraduated in different

Universities and colleges.

Basically the Ethiopian

education policy always

focuses on quantity than

quality. Even if these

number of students get

graduated, there is no job

opportunities in the

country and because of

this most of these

graduates remain addicted

to alcohol and drugs

finally insulted by the

government as loiter.

What else choice the

young and vibrant

generations would have?

What shall we do!!! To

be continued............

Weyane (TPLF)

und die

Verfassung

Rodas Tesfaye Langen(Hessen),

Germany

Mit der Spaltung von

Stämmen gelingt Weyane

(TPLF) die Menschen in

einem Land gegenseitig

zum Kampf zu bringen.

Die Spaltung hatte bei

den bisherigen

äthiopischen Geschichten

nie gegeben.

TPLF gibt den Menschen

neue Identitäten, wo nur

eine Volksgrupp die

Führungsposition

übernommen hat und

über die anderen herrscht.

Die Aufteilung der

Ethenien welches Weyane

erfunden hat, ist auf dem

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

17 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

weg das Land in eine

großen Absturz zu

geraten. Selbst an die

Verfassung das TPLF

nach seinem Geschmack

für sich geschrieben hat

kann sich noch nicht mal

daran halten.

Hier sind einige

Paragraphen der

Verfassung an denen sich

TPLF nicht einhalten

könnte

[11/07 00:53] Netsi:

1)Paragraph 5 über

Sprachen

5.1. Die sämtlichen

Sprachen in Äthiopien

genießen gleichwertige

Anerkennung seitens der

Staates

5.2.Amharisch ist die

Arbeitssprach der

Bundesregierung

5.3. Die föderal

Bundesländer dürfen

deren eigenen

Arbeitssprache mit der

Rechtsordnung.

Schauen wir uns mal

Paragraph 5.1.und 5.3.

genauer an.

5.1. " Die sämtlichen

Sprachen in Äthiopien

genießen gleichwertige

Anerkennung seitens der

Staates"Diese Aussage ist

von der Wahrheit weit

entfernt.Eine Volksgruppe

nutzt sogar die Sprache

dazu aus, um die

restlichen Stämmen

einzuschüchtern. Die

Menschen, die diese

Volksgruppe angehören,

sind die höchsten

Offiziere des Landes und

haben Vorrang in der

Gesellschaft.

[11/07 00:54] Netsi: 5.3.

"Die föderal

Bundesländer dürfen

deren eigenen

Arbeitssprache selbst

bestimmen".

Hierdurch würden die

Bürger blockiert, sich von

Ort zu Ort in ihren

eigenen Mutterland zu

bewegen, weil die

einzelnen Bundesländern

nochmal selbstständig

Arbeitssprache bestimmt

haben obwohl amharisch

die Amtssprache des

ganzen Landes ist. Man

ist z.B nicht in der Lage

ein Hotelzimmer

außerhalb seine Regions

zu buchen oder

medizinische

Versorgungen zu

bekommen weil man sich

mit den Leuten dort nicht

verständigen kann.

Paragraph 10.

Demokratische und

Menschenrechte

10.1. Die würde des

Menschns ist unantastbar

10.2. Bürger,

Menschenrechte und

demokratischerechte

werden eingehalten.

[11/07 00:54] Netsi:

Wenn wir uns die Punkte

10.1 und 10.2

Betrachten, sehen wir

was wicklich Weyane aus

der Verfassung daraus

macht.

Trotz dass man diese

Rechte von Geburt an

hat, werden viele

Menschen gequält und

sogar ermordet.

Äthiopien hat mehrmals

weltliche Verträge

unterschrieben. Unter

diesem befindet sich das

Grundgesetz.

TPLF missachtet diese

weltweite Gesetze und

lässt die Menschen

darunter leiden. Obwohl

Weyane auch mehrmals

Warnungen von anderen

Länder und Amnesty

International bekommen

hat, ignorierte die

diktatorische Partei

TPLF.

Paragraph 11. Trennung

zwischen Religion und

Staat

11.1. Regierung und

Religion sind getrennt

11.2. Es gibt keine

staatlichen Religion

11.3. Die Staat mischt

sich nicht in religiöse

Angelegenheiten ein.

[11/07 00:55] Netsi:

Äthiopien hat eine große

Tradition von

respektvollen Umgang

miteinander

gehabt.Seitdem aber

Weyane die

Führungsposition

übernommen hat, haben

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

18 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

die Menschen das

gegenseitiges Tolerierung

verloren. Die Staat mischt

sich in religiöse

Angelegenheiten ein,

richtet die Leute, die im

Bereich des Religions

arbeiten nach TPLF

Willen alles zu tun.

Wer dagegen etwas

unternimmt wird von der

diktatorischen

Bundesregierung

verhaftet oder ermordet,

denn bei denen spielt die

Freiheit eines Religions

keiner Rolle.

Paragraph 12.

Arbeitsleistung und

Verantwortung der

Bundesregierung

12.1. Die Menschen

wissen was die Staat tut

[11/07 00:55]

Netsi: 12

.2. Eine der durch eine

Wahl gewählte Beamte

wird wieder abgewählt

wenn die Menschen das

Vertrauen verlieren, dass

er seine Verantwortung

nicht übernehmen kann

sagt die Verfassung. Die

Offizier, die von der

diktatorischen Partei

TPLF eingesetzt wurden,

lagern Geld für sich

welches der Menschen

des Landes gehört und

werden auch nicht

angeklagt. Im Gegensatz

werden die restlichen, die

unter diese Beamten nicht

mehr unter leiden wollen

diskriminiert und

verfolgt. Man sieht

hier unter die oben

genannten wenigen

Paragraphen, dass TPLF

der seit 24 Jahre das

ganze Land unter einem

Stamm im Griff hat,eine

Verfassung geschrieben

hat wobei ein paar Sachen

sehr kritisch sind und den

noch nicht in der Lage si

zu befolgen.

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

19 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

ስነ ግጥም

አርበኛ የሚያሰኝህ

Tesfaye Gebreyohannes Abraha

Eppertshausen, Germany

ኣርበናኛ የሚያሰኝህ ላንተ ቁም ነገሩ የህዳሴ ግድብ ብሎ መዘመሩ ይህ ነው ቁም ነገሩ ላንተ ጀግንነቱ ህጻናትን ገድሎ እሬሳ ተራምዶ ዉስኪ መራጨቱ ማንነት ማዋረድ ማንነት ማንጓተቱ ቁም ነገሩ ላንተ ሰዉን መዘርጠጡ የማንም ሰው ችግር ከኣባይ ግድብ ኣይደል ወይ ከሃገሩ ያንተ ጓደኞች ከብረው በፎቅ ቤት ሲኖሩ ጮማ እየቆረጡ ከቆንጆ ሲዳሩ ሚሊዮኖች ተርበው በችግር ተጠብሰው ከትርፍራፊ ጉርሻቸዉን ገዝተው እግረኛ መንገድ ላይ ካርቶኑን ኣንጥፈው ባረረ ኣንጀታቸው ሙቀትና ብርዱ ተፈራርቆባቸው ይህንን ማየት ነው ላንተ ቁም ነገሩ ላንተ ጀግንነቱ ይህንን ማየት ነው ላንተ ቁም ነገሩ ላንተ ጀግንነቱ ያንተ ሹማምንቶች ቢሮኣቸዉን ዘግተው በየቢሮው ደጃፍ ባለ ጉዳቱ ይ ትተው ህዝብ እንደሚያጉላሉ ይህ ላንተ ተፍቶህ ነው የቱ ነው ጥፋቱ የቱ ነው ዉሸቱ የቱ ነው ጥፋቱ የቱ ነው ዉሸቱ ካገሬው ሰው ይልቅ ለውጭው ማጎብደዱ ከዉጭ ለመጣው ቱጃር ማጎብደዱ ይሄ ነው ክደቱ ይሄ ነው ዉሸቱ

ድምጽ የሌለው ጥይት

Dawit Kasahun, Germany

ድምጽ የሌለው ጥይት የወያኔ ስር ኣት ድምጽ በሌለው ጥይት ኣፋችን ኣፈኑት ድምጽ በሌለው ጥይት እጃችን ኣሰሩት ኣንድ ለኣምስት ብለው ህዝባችን ከፈሉት ኣማራ ኦሮሞ ጉራጌ እያሉት የበስ ተመልካች ህዝባችን ኣረጉት ከጥንት ከጥዋቱ ኣንድ ናት ኢትዮጵያ እንዲህ ያለማ ወጣት ልቅም ትፍር ኣድርገው መጣል ነው ኣስር ቤት ጋዜጠኛው ኮርቶ በሙያው ለመስራት ያየሁትን እዉነት እጽፋለሁ ብሎ ብእሩን በማንሳት ኣንብበው ይረዱ የኢትዮጵያ ልጆች ይሕንማ እውነት ኣንደዚህ ከኣልክማ እጆችህን ኣስረው ኑሮህ ወደ ኣስር ቤት ተነሱ እንነሳ በኣንድነት ሆነን እጅ ለእጅ ተያይዘን የኣረመኔን ስር ኣት መገርሰስ ኣለብን ላዩ ዴሞክራሲ ውስጡ ኣፈና እንግልት እስከመቼ እንኑር በእንዲህ ያለ ስር ኣት እዩልን ስሙልን የኣለም መንግስታት ማራዘሚያ ኣንሁን የወያኔን ስር ኣት

ዱላ ቅብብል (ለአሁኑ

ገዢዎቻችን) Tiraza Tsiga

(Frankfurt, Germany )

ድንቅ ያፍሪካ አትሌቶች የሚሰሩት ስራ መላውን ጥቁር ህዝብ እጅግ ስላኮራ በየደረሱበት በየውድድሩ ታሪክ እየሰሩ ድል እያበሰሩ የናት ምድራቸውን ስም ስላስከበሩ ለታላቅ ስልማት ወደ አፍካ አዳራሽ በክብር ተጠሩ: ከዚያም ጋዜጠኛ ተናግሮ አናጋሪ የወሬ ሱሰኛ ወደ አንዱ አትሌት ቀርቦ አድናቆቱን ገልፆ ድምፁን አለዝቦ

"ፅናት በሚጠይቅ ረዥም ርቀት ታሸንፋላችሁ ሁሌም ያለጭንቀት አምስት ሺ አስር ሺ ውጤቱ ቢያረካም ዱላ ቅብብሉስ ለምን አይሳካም?" በማለት ጠየቀ ታዋቂው አትሌትም በስሱእየሳቀ "ቀን ከሌት በመስራት ውጤታችን አምሮ ጥረታችን ሰምሮ በስካሁን ድላችን ረክቷል ህዝባችን ዌል እንግዲህ ደሞ ዱላ ቅብብሉን ለመሪወቻችን" ብሎ ተናገረ በዚህ ንግግሩም ሪከርድ ሰበረ::

ፍትህን ፍለጋ

Solomon Worku Schwalbach, Germany

ጥላቻን የዘራች ቂምን ያበቀለች፣ የወያኔ መንግስት ህዝብን ያማረረች፣ ተማሪን ያሰረች ጋዜጠኛ አፍና ተኩሳ ገደለች። ሙስሊም ክርስትያኑን ደብድባ ቂሊንጦ ያሰረች፣ የመለስ ዕራዕይ ዕንዲያው ስትታወቅ ስንቱን አማረረች። ዲቃላ ልጅ ዲቃላ ወለደች፣ ምናለ ያን ጊዜ ሽል ሆና በቀረች። ጥላቻን የዘራች አማራን ነው ትግሬ ነው ደቡብ ነው ኦሮሞ ነፍጠኛ ዕያላሁ፣ ዕንዳው በዕንጉርጉሮ ዜማ ዕያዜማች ሁ፣ ህዝቤን ዕንጨት ዕየሰነጠራችሁ፣ ዕናንተ ወያኔ ዕንዳው ምን ተሻላችሁ። ሀይ ባይ ብታጡ ተናግሮ የሚሰማ፣ ፈጣሪ ዕንደሰው ድምጽህን አሰማ። ልዚች ምስኪን ሀገር ፍት ህ ለተጠማች፣ አሳያት ክንድህ ን አለሁልሽ በላት።

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

20 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

ስቃያቸው በዛ ዕረ የወገኔ፣ ስራም የለም አሉ ካልሆኑ ወያኔ። አልኖርም ለሆድ ክብሬ ዕየተቀማ፣ ዕኔም ዘረጋሁኝ ሰጭው ካልተቀማ።

ነጻነት በብላሽ

(ሄኖክ የሺጥላ) የምን ነጻ እንውጣ ገንዘቤን ሰብስቤ ጭኔ እስክወጣ አልፈልግም ጣጣ !

እስካለሁኝ ድረስ መቶ እጅ የኔ ነው ሞቶ ሞቶ ሞቶ አንተ መሪ ልትሆን ፣ አትችልም ከቶ

የዘመናት ብሶት ፣ ጸንሶ ና ወልዶኝ ገና ቁሜ ሳልሄድ ፣ የምን ወግድልኝ ይመስልሃል እውነት ፣ በምርጫ

እምወጣ ይመስልሃል እንደው ፣ ካርታ

የምጠጣ ገንዘቤን ዘርፌ ፣ ቀምቼ ሳልወጣ ?

የኔ ነው ሃገሩ ፣ የኔ ነው ሰፈሩ አቅም ካለህ ቀማ እኔም ቀምቼ ነው ያኔ ብቻ ያኔ ያኔ እለቃለሁ ! እንጂ በስብሰባ በሰላማዊ ሰልፍ አትሞክረው ተወው ይሄን ተራ ዘራፍ ! ነገርኩህ ደግሜ በመቶ እጅ ድል ቀልድ አላውቅም እኔ ትገባለህ ገደል !

ተራራ ደርምሼ ያመጣሁትን ድል አንተ በስክርቢቶ ፣ ጽፈህ ልትቀበል

ቅማል ተሸክሜ ያመጣሁትን ድል አንተ በኮሮጆ ፣ በእጣ ልትጥል ?

ሞኝ ነህ ፣ ከረፈፍ ጅላንፎ ፣ ቂላቂል የማየረባ ጩኸት ያህያ ላይ ደውል !

ይልቅ ነጻነቱ ፣ መከበር ካማረህ ቀማ ብዬሀለው ፣ ውርደት ካሳፈረህ

ነገርኩህ እኮ እኔ ሊማልሞን ውጣ እሾህ በሾህ እንጂ ፣ በሽኮኮ ላይወጣ እንጂ በልምምጥ በእግዚኦታ ፣ ስልጣን እኛ በዚያ ዋጋ መች ገዝተን አስመጣን

እያልክ ያለኸው ፣ እኔን እንደገባኝ በብላሽ ሽጥልኝ ፣ በብላሽ አስወጣኝ አያዋጣም አንተ ቁረጥና ክተት ቁረጥና ግባ ያንተ ድምጽ እሱ ነው ለኔ የሚገባ !

ጎሕ መጽሔት ሐምሌ 2007 ዓ. ም. 2ኛ አመት ቁጥር 10

21 Goh magazine, July 2015, 2nd edition, No. 10

አስደሳች ዜና: በጀርመን የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ምክር ቤት ህጋዊ ማህበር እውቅና አግኝቶ ተመሰርተ

Äthiopischer Migrationsrat in Deutschland .e.v (Verein)

ይህ ማህበር የተቋቋመበት ዋናው ዓላማ እና ተግባሩ በተለያዩ ምክንያቶች አገራቸውን ትተው ለተሰደዱ እና የተለያየ ችግር ለሚደርስባቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ፈጥኖ መድርስ እና የህግ ከለላ እዲያገኙ ከኢትዮጵያውያን ጎን መቆም ነው። ስለዚህ ይህ ማህበር ተጠናክሮ ለቆመለት ዓላማ ስኬታማነት ለውጤት እንዲበቃ

ከኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አገር ወዳዶች ከሆኑት ሁሉ ማንኛውንም ድጋፍ ይፈልጋል። 50

ሎሜ ለ50 ሰው ጌጡ ነው ለአንድ ሰው ግን ሸክም ነው እደተባለው ሁሉ እስካሁን ለቆምንለት ዓላማ ከጎናችን ሁናችሁ ስትታገሉ እና ሥትታግሉ ለነበራችሁ እና እንዲሁም በቅርብ ርቀት ሁናችሁ ስትከታተሉ ለቆያችሁ ውድ ወገኖቻችን በሙሉ ለዚህ ለተቀደሰ ዓላማ ድጋፋችሁን እድትለግሱ በክብሮት እንጠይቃለን። ስለዚህ የተቻለዎትን

ከለገሱ ሰው ለወገን ያለውን ከወረወረ 50 ሎሚ ለ50 ሰው ሆነ ማለት ነው።

ማሳሰብያ: ይህን መልዕክት ተርድታችሁ ለመርዳት የምትፈልጉ ሁሉ የድጋፍ መሥጫው ዘዴ እደሚከተለው ተገልጿል።

Subject: To support Ethiopian Migrations Counsel financially in Germany

Äthiopischer Migrationsrat in Deutschland e.v

Bank Contacts = Bank Sparkasse

Account Number.16094435

Bank sort Code-50852553

IBAN: DE41508525530016094435

Bank Code (BIC):HELADEF1GRG

Bank verbindung: Sparkasse

Konto Nummer.16094435

Bankleitzahl 50852553

IBAN:- DE41508525530016094435

Bank Code (BIC):HELADEF1GRG

ውድ የጎሕ መፅሔት አንባቢያን

ጎሕ ቁጥር 11 ዕትሟ October 30/2015 ስለሚወጣ አስተያየትና መጣጥፍ መላክ የምትፈልጉ የፁሁፍ የመላኪያ ቀን እስከ October 15 ድረስ መሆኑን

በአክብሮት እንገልፃለን። አድራሻ: Desalegne Abebew

Büdesheimer Str. 9

61137 Schöneck

ስልክ: 015120475458, 01521374981 015219261884